Monday, 28 March 2011

ሀገሬ


     ሀገሬ
እዚያ ዘመድ አለ
ሁሉም የእናት ልጅ ነው
ሁሉም የአባት ልጅ ነው
ጠላትም አንዳንዴ ይመጣል መቃብር
ባለጋራም ቸር ነው ያገር ልጅ ሲቸገር
መቅደስ ነው አገሬ
አድባር ነው አገሬ
እሾህ ነው አገሬ
በጀግናው ልጅ አጥንት የተከሰከሰ
ጠላት ያሳፈረ አጥቂን የመለሰ
አገሬ ታቦት ነው መቅደስ የሃይማኖት
ዘመን የፈተነው በጠበል በፀሎት
ለምለም ነው አገሬ
ውበት ነው አገሬ
ገነት ነው አገሬ
ብሞት እሄዳለሁ ከመሬት ብገባ
እዚያ ነው አፈሩ የማማ ያባባ
ስሳብ እሄዳለሁ ቢሰበርም እግሬ
አለብኝ ቀጠሮ
ከትውልድ አገሬ ካሳደገኝ ጓሮ::
            በገብረክርስቶስ  ደስታ/ 1953/

No comments:

Post a Comment